ኣዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በኣገሪቱ ብሔራዊ እርቅ ለማምጣት የሚስሩ ከሆነ፤ በሲዳማው የሎቄው እልቂት ተሳታፊ የሆኑ የመንግስት ባለስልጣናትን ለፍርድ ያቅርቡ
ኣዲሱ
ጠቅላይ ሚኒስትር በኣገሪቱ ባለው የመልካም
ኣስተዳደር ችግር ብሎም የኣገሪቱ ሕገ መንግስት
በሚፈቅደው መልኩ የተለያየ ሰብኣዊ መብቶቻቸውን
በሰላማዊ መንገድ በመጠያቃቸው ብቻ፤ በጸጥታ
ኃይሎች ግፍ ለደረሰባቸው ሰለባዎች፤ የተሰማቸውን
ልባዊ ሀዘን እና ይቅርታ ከመጠየት ኣልፈው፤
የድርጊቱን ፈጻሚዎች ለህግ መቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
ከጥቂት
ዓመታት በፊት፤ በሲዳማ ውስጥ በነበረው
የመልካም ኣስተዳደር ችግር ብሎም ራስን በራስ
የማስተዳደር ሕገ መንግስታዊ መብትን በጠየቁ
የሲዳማ ተወላጆች ላይ የሞት እና የኣካል ጉዳት
ያደረሱ ብሎም ድርጊቱን በበላይነት ኣመራር
በመስጠት የተሳተፉ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር
ኣቶ ኃይለማርያም ደሳሌኝን ጨምሮ በኣሁኑ
ጊዜ በከፍተኛ የመንግስት ኣስተዳደር የተሰገሰጉ
የኢህኣዴግ ኣመራር ለፍርድ እንድቀርቡ ማድረግ
ይጠበቅባቸዋል።
በወቅቱ
የነበረውን ሰቆቃ በተመለከተ፤ ከዚህ በፊት
ኣቅርበነው የነበረውን ዝርዝር ዘገባ ከታች
ልንኩን ተጨነው ያንቡ፦ የግንቦቱ ዕልቂት
Comments
Post a Comment